Wednesday, December 10, 2014

Galatians ch.2

                               EVALUATE OUR SELVES!

Galatians Chapter 2 verse 1 says that 'After 14 years he/Paul/ went up again to Jerusalem with Barnabas and Titus.' I ask you why Paul went up to Jerusalem again? why? the answer is because God revealed some thing to him.The bible says that he went up by revelation or NIV says 'response to revelation'. The revelation was that God showed or told him that 'I was running or had run my race in vain'.

Paul was true minister,he experienced real salvation,he had good relationship with the Lord...he was serving the Gospel in different countries and areas....he had many spiritual qualities as well.But still he needed to check himself and his ministry too.

If Paul did like this,we need to check our all life activities and stands before God.Brothers and sisters we need to check our selves always.For example after 21 days we will receive the New year from God......before that we have to evaluate our past life and activities like a trader.we have to know our weighed /pounds or kilos/.

WHAT WAS LIKE THAT OUR LIFE FOR THE PAST YEARS? AT LEAST 2014?

Examine our selves and improve our love,perseverance,motive......ministry/all life activities.If it was bad thing all the past life....at least we can to redeem our future.

May the Lord help us!

benjabef@gmail.com



Sunday, November 9, 2014

አራቱ ጨረቃዎች / ክፍል -2/

                                      አራቱ ጨረቃዎች -ክፍል ሁለት

በክፍል አንድ ላይ እንደተመለከትነው ጨረቃዎች ወይም ጸሀይ ወይንም ከወዋክብቶች በሚያሳዩት ለየት ያሉ ምልክቶቻቸው ለእስራኤል እና ለዓለም የሚያሰተላልፉት ብርቱ መልዕክት እንዳለ ግልጽ ነው፡፡ የእግዚአብሄር ቃል በ ዘፍጥረት 1 ቁጥር 14 ላይ ሲናገር "እግዚአብሔርም አለ ቀንና ሌሊቱን ይለዩ ዘንድ ብርሀናት በሰማይ ጠፈር ይሁኑ፤ለምልክቶች ፡ለዘመኖች ፡ለዕለታት ለዓመታትም ይሁኑ፡፡'' ቃሉ ላይ ከላይ እንደተመለከተው 'ለምልክቶች' ይላል....ይህ ማለት ብርሀናቱ የሰው ልጆችን ስለ አንዳች ጉዳይ ከ እግዚአብሔር ዘንድ ሊደረግ ስላለ ነገር እንዲጠቁሙ ና ምልክት እንዲሰጡ የሚናገር ነው፡፡ በማቴዎስ ወንጌል ላይ እንደተጻፈው የጌታችን የኢየሱስ ከክርስቶስ መምጫው ምልክቱን ከሚናገሩት መካከል እነዚህ ብርሀሃናት ዋነኞቹ ናቸው--"ከዚያች ወራት መከራ በኋላ ወዲያው ጸሐይ ይጨልማል ጨረቃም ብርሀኗን አትሰጥም ፤ክዋክብትም ከሰማይ ይወድቃሉ የሰማይ ሀያላትም ይናወጣሉ፡፡በዚያን ጊዜ የሰው ልጅ ምልክት በሰማይ ይታያል::"/ 24 ቁ 29/፡፡

ሉቃስ በሐዋርያት ሥራ 2፡17-20 ላይ እንደጠቆመው እግዚአብሄር በመጨረሻ ዘመን ከሚያደርጋቸው ነገሮች እና የጌታን ቀን መድረስ ከሚያመለክትበት ነገር ውስጥ ፀሐይ ወደ ጨለማ ጨረቃም ወደ ደም መቀየራቸው ጉዳይ ነው፡፡ መቼም ይህ  ሁሉ ጉዳይ ዝም ብሎ ሊሆን አይችልም፡፡ በባለፉት ዘመናት በነበሩ ክስተቶችም በዓለም ዙሪያ ጉልህ ነገሮች ተፈጽመዋል፡፡

ስለዚህ ነው ከናሳ በላይ የጨረቃና የፀይሐን ጉዳይ በብርቱ መከታተል ተገቢ የሚሆነው፡፡ እግዚአብሔር ብርሀናቱን ምልክት አድርጓቸዋልና...የእነሱ ለውጥ በአየር መበከልና ለሌሎች ሰው ሰራሽ ተጽዕኖ አመጣው ከሚባለው ነገር በላይ ነው፡፡ሙቀትና ብርሀንን ከመስጠትም ያልፋል፡፡ ብዙ ጊዜ ወቅቶች ስለ መፈራረቃቸውና ከላይ የተዘረዘሩትን ጥቅሞች ስለሚሰጡበት ጉዳይ ላይ ብቻ ብናተኩር ለመጨረሻው ዘመን ሁኔታ የሚያስተላልፉትን መልዕክት ተረድተን ልንጠቀምባቸው አንችልም፡፡
ብርሀናቱ ላይ የሚሆነውን ክስተት ሁሉ ብንከታተል ግን እግዚአብሄር አምላክ በመጨረሻው ዘመን ሊጠቁመን ከሚፈልገው ና ሊያደርገው የወሰነውን ሐሳቡን እንዲሁም፣ስለ ዋናው የልጁ የጌታችን የኢየሱስ ከክርስቶስ መገለጥን ሁኔታ ብዙ ልናውቅ እንችላለን፡፡

ተጨማሪ ጥቅሶች፡- መዝ.104፡19 ፤ ኢሳ.13፡10፤ ራዕይ 6፡12 ፤ ሉቃ.21፡25 ማንበብ ይችላሉ፡፡

በሚቀጥለው ጊዜ እነዚህ ምልክቶች በተለያየ ጊዜ ሲከሰቱ የእኛ ድርሻ ከሕይወት ፡ ከትጋትና ወንጌልን ከመመስከር ደግሞ ጌታችንን ተዘጋጅቶ ከመጠበቅ አንጻር ከእግዚአብሄር ቃል እንማራለን፡፡ ጌታ በነገር ሁሉ ማስተዋልን ይስጠን፡፡ አሜን፡፡ እነሆ ጌታ ኢየሱስ በቶሎ ይመጣል፤

                                                                                                           benjabef@gmail.com

Sunday, November 2, 2014

አራቱ ጨረቃዎች / ክፍል-1/

                  አራቱ ወደ ደምነት  ተለውጠው የሚወጡ ጨረቃዎች   በ /2014 እና 2015 እ.አ..አ/



     በ 2014/15 እ.ኤ.አ. አራቱ ጨረቃዎች ወደ ደምነት  ተለውጠው እንደሚወጡ የአሜሪካ የጠፈር ምርምር መዐከል ባለፉት ጊዜያት ይፋ ማድረጉ ይታወቃል፡፡የክስተቶቹ ጊዜያት በትንበያው መሰረት ሚያዚያ 15 እና ኦክቶበር  8 /2014 ሲሆን  ዕለታቱ የአይሁድ ፋሲካ እና የዳስ በዐል/feast of Tabernacle/ ላይ የሚውል ነበር ይህም ታሪካዊ ክስተት በትንበያው መሰረት በቅርቡ ተፈጽሙዋል፡፡ የቀሩት ሁለቱ ጨረቃዎች ደም ለብሰው የሚከሰቱበት ጊዜ የፊታችን አደሱ የ አውሮፓውያን ዓመት ኤፕሪል 14 እና ሴፕቴምበር 28 /2015 ነው ተብሎ ይጠበቃል፡፡ ይህም በድጋሚ የአይሁድ ፋሲካ እና በታላቁ የዳስ በዐላቸው ዕለታት መሆኑ የሆነ አንድ ነገር ከእግዚአብሄር ዘንድ  የሚያመለክተው ነገር እንዳለ የሚያጠራጥር ነገር አይደለም፡፡
/በዚህ ጉዳይ በተለይ የ ጆን ሀጌን መጽሐፍ ቢያነቡ ጥሩ ነው፡፡/

ከዚህ በፊት ጨረቃ ወደ ደም ተለውጣ የወጣችባቸው ዓመት ነበሩ ለምሳሌ፡-
በ 1493-94 /እ..ኤ.አ./  ላይ ተከስቶ ነበር፡ በጊዜውም እስፔን የወደቀችበት፣ ለእስራኤላውያን የመከራቸው ጊዜ ነበር ፤ከዚህም ሌላ ኮሎመቦስ ታላቁዋን አሜሪካንን ያገኘበት ወቅት ሆኖ አለፈ፡፡
በ 1948-49 እ.ኤ.አ. ደግሞ በተከሰተበት ወቅት እስራኤል እንደ አገር ለዐለም ያወጀችበት ወቅት ነበር፡፡

  እ.ኤ.አ.በ 1967-68  ላይ ከጨረቃዋ ክስተት በሁዋላ እስራኤል በዐረቦች ከተከበበችበት ድንገተኛ ከበባ የ ስድስት ቀን ብርቱ ጦርነት አድርጋ በእግዚአብሄር እርዳታ በድል ያጠናቀቀችበት ወቅት ሆኖ አልፉዋል፡፡
አሁን ደግሞ ባለንበት በዚህ ጊዜ ምን ሊከሰት እንደሚችል በእርግጠኝነት መናገር ባይቻልም የሆነ ነገር ግን ሊሆን እንደሚችል አመላካች ሁኔታዎች አሉ፡፡ ለነገሩ ከ ኤፕሪል 15/2014 ክስተት በሁዋላ በእስራኤልና በዓለም ዙሪያ እየሆነ ያለውን ነገር መመልከት ብቻ በቂ ሊሆን ይችላል፡፡

እስራኤል በሶሰቱ ወጣት ዜጎችዋ መገደል ምክንያት ለበቀል የወሰደችው ርምጃ እስካሁን ለበርካታ ወራት ያለቆመ ከመሆኑ ባሻገር ሺዎች የሞቱበት እና ከፍተኛ ውድመት የተደረገበት ነው፡፡በ ዓለም ላይ ቢሆን አይሲስ የሚባል አክራሪ የእስልምና ቡድን ተነስቶ ምድር በአሰቃቂ ሁኔታ ላይ ትገኛለች፡፡በዚሀም ላይ ኢቦላ የሚባል ከባድ ወረርሽኝ ተከስቶ ዐለመም ሁሉ ከፍተኛ ስጋት ላይ ነች፡፡እነዚህን ለ አብነት ያህል ይጠቀስ እንጂ እየተከሰቱ ያሉት ክፉ ሁኔታዎች በርካቶች ናቸው፡፡

ለመሆኑ ስለ ጨረቃ ወደ ደም መቀየር ክሰተት መጽሐፍ ቅዱስ ምን ይላል ?ምን ትንቢትስ ተነግሩዋል.??......የሚሉትን ነጥቦች በ ቀጣይ ጊዜ እናነሳለን፡፡ ነገር ግን አሁን ከመቼውም ጊዜ ይልቅ መጨረሻው ጊዜ ላይ እንዳለን አውቀን ራሳችንን በፊቱ በንስሀ እንድናቀርብ እመክራለሁ፡፡ እነሆ ጌታ በደጅ ነውና፡፡


                                                                                                      benjabef@gmail.com

Thursday, October 23, 2014

   "..And we know that all things work together for good to them that love God ,to them who are  the called according to his purpose'' Rom.8:28

Saturday, October 18, 2014

This is my first blog that I am excited about to share my thoughts!

Many Blessings!