Sunday, November 9, 2014

አራቱ ጨረቃዎች / ክፍል -2/

                                      አራቱ ጨረቃዎች -ክፍል ሁለት

በክፍል አንድ ላይ እንደተመለከትነው ጨረቃዎች ወይም ጸሀይ ወይንም ከወዋክብቶች በሚያሳዩት ለየት ያሉ ምልክቶቻቸው ለእስራኤል እና ለዓለም የሚያሰተላልፉት ብርቱ መልዕክት እንዳለ ግልጽ ነው፡፡ የእግዚአብሄር ቃል በ ዘፍጥረት 1 ቁጥር 14 ላይ ሲናገር "እግዚአብሔርም አለ ቀንና ሌሊቱን ይለዩ ዘንድ ብርሀናት በሰማይ ጠፈር ይሁኑ፤ለምልክቶች ፡ለዘመኖች ፡ለዕለታት ለዓመታትም ይሁኑ፡፡'' ቃሉ ላይ ከላይ እንደተመለከተው 'ለምልክቶች' ይላል....ይህ ማለት ብርሀናቱ የሰው ልጆችን ስለ አንዳች ጉዳይ ከ እግዚአብሔር ዘንድ ሊደረግ ስላለ ነገር እንዲጠቁሙ ና ምልክት እንዲሰጡ የሚናገር ነው፡፡ በማቴዎስ ወንጌል ላይ እንደተጻፈው የጌታችን የኢየሱስ ከክርስቶስ መምጫው ምልክቱን ከሚናገሩት መካከል እነዚህ ብርሀሃናት ዋነኞቹ ናቸው--"ከዚያች ወራት መከራ በኋላ ወዲያው ጸሐይ ይጨልማል ጨረቃም ብርሀኗን አትሰጥም ፤ክዋክብትም ከሰማይ ይወድቃሉ የሰማይ ሀያላትም ይናወጣሉ፡፡በዚያን ጊዜ የሰው ልጅ ምልክት በሰማይ ይታያል::"/ 24 ቁ 29/፡፡

ሉቃስ በሐዋርያት ሥራ 2፡17-20 ላይ እንደጠቆመው እግዚአብሄር በመጨረሻ ዘመን ከሚያደርጋቸው ነገሮች እና የጌታን ቀን መድረስ ከሚያመለክትበት ነገር ውስጥ ፀሐይ ወደ ጨለማ ጨረቃም ወደ ደም መቀየራቸው ጉዳይ ነው፡፡ መቼም ይህ  ሁሉ ጉዳይ ዝም ብሎ ሊሆን አይችልም፡፡ በባለፉት ዘመናት በነበሩ ክስተቶችም በዓለም ዙሪያ ጉልህ ነገሮች ተፈጽመዋል፡፡

ስለዚህ ነው ከናሳ በላይ የጨረቃና የፀይሐን ጉዳይ በብርቱ መከታተል ተገቢ የሚሆነው፡፡ እግዚአብሔር ብርሀናቱን ምልክት አድርጓቸዋልና...የእነሱ ለውጥ በአየር መበከልና ለሌሎች ሰው ሰራሽ ተጽዕኖ አመጣው ከሚባለው ነገር በላይ ነው፡፡ሙቀትና ብርሀንን ከመስጠትም ያልፋል፡፡ ብዙ ጊዜ ወቅቶች ስለ መፈራረቃቸውና ከላይ የተዘረዘሩትን ጥቅሞች ስለሚሰጡበት ጉዳይ ላይ ብቻ ብናተኩር ለመጨረሻው ዘመን ሁኔታ የሚያስተላልፉትን መልዕክት ተረድተን ልንጠቀምባቸው አንችልም፡፡
ብርሀናቱ ላይ የሚሆነውን ክስተት ሁሉ ብንከታተል ግን እግዚአብሄር አምላክ በመጨረሻው ዘመን ሊጠቁመን ከሚፈልገው ና ሊያደርገው የወሰነውን ሐሳቡን እንዲሁም፣ስለ ዋናው የልጁ የጌታችን የኢየሱስ ከክርስቶስ መገለጥን ሁኔታ ብዙ ልናውቅ እንችላለን፡፡

ተጨማሪ ጥቅሶች፡- መዝ.104፡19 ፤ ኢሳ.13፡10፤ ራዕይ 6፡12 ፤ ሉቃ.21፡25 ማንበብ ይችላሉ፡፡

በሚቀጥለው ጊዜ እነዚህ ምልክቶች በተለያየ ጊዜ ሲከሰቱ የእኛ ድርሻ ከሕይወት ፡ ከትጋትና ወንጌልን ከመመስከር ደግሞ ጌታችንን ተዘጋጅቶ ከመጠበቅ አንጻር ከእግዚአብሄር ቃል እንማራለን፡፡ ጌታ በነገር ሁሉ ማስተዋልን ይስጠን፡፡ አሜን፡፡ እነሆ ጌታ ኢየሱስ በቶሎ ይመጣል፤

                                                                                                           benjabef@gmail.com

Sunday, November 2, 2014

አራቱ ጨረቃዎች / ክፍል-1/

                  አራቱ ወደ ደምነት  ተለውጠው የሚወጡ ጨረቃዎች   በ /2014 እና 2015 እ.አ..አ/



     በ 2014/15 እ.ኤ.አ. አራቱ ጨረቃዎች ወደ ደምነት  ተለውጠው እንደሚወጡ የአሜሪካ የጠፈር ምርምር መዐከል ባለፉት ጊዜያት ይፋ ማድረጉ ይታወቃል፡፡የክስተቶቹ ጊዜያት በትንበያው መሰረት ሚያዚያ 15 እና ኦክቶበር  8 /2014 ሲሆን  ዕለታቱ የአይሁድ ፋሲካ እና የዳስ በዐል/feast of Tabernacle/ ላይ የሚውል ነበር ይህም ታሪካዊ ክስተት በትንበያው መሰረት በቅርቡ ተፈጽሙዋል፡፡ የቀሩት ሁለቱ ጨረቃዎች ደም ለብሰው የሚከሰቱበት ጊዜ የፊታችን አደሱ የ አውሮፓውያን ዓመት ኤፕሪል 14 እና ሴፕቴምበር 28 /2015 ነው ተብሎ ይጠበቃል፡፡ ይህም በድጋሚ የአይሁድ ፋሲካ እና በታላቁ የዳስ በዐላቸው ዕለታት መሆኑ የሆነ አንድ ነገር ከእግዚአብሄር ዘንድ  የሚያመለክተው ነገር እንዳለ የሚያጠራጥር ነገር አይደለም፡፡
/በዚህ ጉዳይ በተለይ የ ጆን ሀጌን መጽሐፍ ቢያነቡ ጥሩ ነው፡፡/

ከዚህ በፊት ጨረቃ ወደ ደም ተለውጣ የወጣችባቸው ዓመት ነበሩ ለምሳሌ፡-
በ 1493-94 /እ..ኤ.አ./  ላይ ተከስቶ ነበር፡ በጊዜውም እስፔን የወደቀችበት፣ ለእስራኤላውያን የመከራቸው ጊዜ ነበር ፤ከዚህም ሌላ ኮሎመቦስ ታላቁዋን አሜሪካንን ያገኘበት ወቅት ሆኖ አለፈ፡፡
በ 1948-49 እ.ኤ.አ. ደግሞ በተከሰተበት ወቅት እስራኤል እንደ አገር ለዐለም ያወጀችበት ወቅት ነበር፡፡

  እ.ኤ.አ.በ 1967-68  ላይ ከጨረቃዋ ክስተት በሁዋላ እስራኤል በዐረቦች ከተከበበችበት ድንገተኛ ከበባ የ ስድስት ቀን ብርቱ ጦርነት አድርጋ በእግዚአብሄር እርዳታ በድል ያጠናቀቀችበት ወቅት ሆኖ አልፉዋል፡፡
አሁን ደግሞ ባለንበት በዚህ ጊዜ ምን ሊከሰት እንደሚችል በእርግጠኝነት መናገር ባይቻልም የሆነ ነገር ግን ሊሆን እንደሚችል አመላካች ሁኔታዎች አሉ፡፡ ለነገሩ ከ ኤፕሪል 15/2014 ክስተት በሁዋላ በእስራኤልና በዓለም ዙሪያ እየሆነ ያለውን ነገር መመልከት ብቻ በቂ ሊሆን ይችላል፡፡

እስራኤል በሶሰቱ ወጣት ዜጎችዋ መገደል ምክንያት ለበቀል የወሰደችው ርምጃ እስካሁን ለበርካታ ወራት ያለቆመ ከመሆኑ ባሻገር ሺዎች የሞቱበት እና ከፍተኛ ውድመት የተደረገበት ነው፡፡በ ዓለም ላይ ቢሆን አይሲስ የሚባል አክራሪ የእስልምና ቡድን ተነስቶ ምድር በአሰቃቂ ሁኔታ ላይ ትገኛለች፡፡በዚሀም ላይ ኢቦላ የሚባል ከባድ ወረርሽኝ ተከስቶ ዐለመም ሁሉ ከፍተኛ ስጋት ላይ ነች፡፡እነዚህን ለ አብነት ያህል ይጠቀስ እንጂ እየተከሰቱ ያሉት ክፉ ሁኔታዎች በርካቶች ናቸው፡፡

ለመሆኑ ስለ ጨረቃ ወደ ደም መቀየር ክሰተት መጽሐፍ ቅዱስ ምን ይላል ?ምን ትንቢትስ ተነግሩዋል.??......የሚሉትን ነጥቦች በ ቀጣይ ጊዜ እናነሳለን፡፡ ነገር ግን አሁን ከመቼውም ጊዜ ይልቅ መጨረሻው ጊዜ ላይ እንዳለን አውቀን ራሳችንን በፊቱ በንስሀ እንድናቀርብ እመክራለሁ፡፡ እነሆ ጌታ በደጅ ነውና፡፡


                                                                                                      benjabef@gmail.com