Friday, July 31, 2015

የሠርግ ጥሪ



      የማክበር ሰላምታችንን እያቀረብን ጌታ ቢፈቅድና ብንኖር በፊታችን ባለው አንድ ቀን ሙሽራው ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሙሽሪትን /ቤተክርስቲያንን/ ከምድር ሊወስዳት ይመጣል፡፡ ልብ ይበሉ የሚመጣበት ሰዐትና ቀን  ባለመገለጹ / ማቴ.24፡36/ ከዛሬዋ ቀን ጀምረው በእውነተኛ ንስሐ ተዘጋጅተው ሙሽራውን ሊጠብቁ ይገባል፡፡ ሙሽራው በሚመጣበት  ያን ጊዜ የዓለም መጨረሻው ይሆናል፡፡ 
       በዚህ ሰርግ ላይ ለመታደም የሚያስፈልጉ መስፈርቶች፡-
1- ነጭ ልብስ መልበስ አለብዎት፡፡ ማቴ 22 ቁ. 11-14 ይህም ንስሐ ገብተው በክርስቶስ ማመንዎትን የሚገልጥ ነው፡፡
2- መብራትና በቂ የሆነ ዘይት መያዝዎትን አይዘንጉ፡፡ ማቴ.25፡1-13
3- ታማኝነትና ልባምነት፡፡ ማቴ.24፡45-51፡፡ ዋና ዋናዎቹ ናቸው፡፡

ታዲያ እርሶ በክርስቶስ ሞትና ትንሳኤ አምነዋልን? እውነተኛስ ንስሐ ገብተዋልን ? ዛሬውኑ ይወስኑ!!!

      Maranatha!

No comments:

Post a Comment