Thursday, January 1, 2015

አራቱ ጨረቃዎች / ክፍል -3 /

ክፍል 3

በባለፉት ተከታታይ ጊዜያት ስለ አራቱ ጨረቃ ደም ለብስው በ 2014 እና 2015 ስለሚወጡበት ሁኔታና መጽኀፍ ቅዱሳዊ ትንታኔ በመጠኑ በመስጠት ነበር ያለፉት ጽሁፍ ላይ የተቀመጠው አነሆ ዛሬ ደግሞ የመጨረሻው ዘመንን በተመለከተ ከእነዚህ ክስተቶች ጋር በማየያያዝ እንቀጥላለን፤

በመጽሐፍ ቅዱስ ላይ በርካታ ቦታዎች ላይ የመጨረሻውን ዘመን በተመለከተ ብዙ የተጻፈ ቢሆንም በተለይ ሊታዩ ከሚችሉ ምልክቶች አንጻር የተጠቀሱትን በተወሰነ መልኩ ባለፈው ክፍል ሁለት ጽሁፍ ላይ ማነሳታችን ይታወሳል፡፡ስለሆነም ከብዙ ምክንያቶች አንጻር አሁን ያለንበት ዘመን የመጨረሻ መጨረሻ ዘመን እንደሆነ አመላካች ነገሮች አሉ፡ ከነዚህም ውስጥ በምድር ላይ ያለው ብርቱ ጦርነት፤ሽብር መስፋፋቱ፤ረሀብና ቸነፈር፤የተፈጥሮ መናጋትና መዛባት.....ለሌሎች ብዙ መከራዎችነን ማንሳት ይቻላል፡፡

ታዲያ በዚህ ወቅት እኛ ምን ማድረግ ይጠበቅብናል?

1-ክርስቶስ ዋጋ የከፈለለትን ውድ ሕይወታችንን በዓለም ጉድፍ ሳናሳድፍ ልንጠብቅ ይገባል፡፡በአሁኑ ጊዜ ሁሉ ነገር አይኑን አፍጥጦ የመጣበት ጊዜ ነው፡፡ድሮ በስውር የነበሩ ነገሮች አሁን አሁን ድብቅ መሆናቸው ቀርቶ የአደባባይ ሆነዋል፡፡ምንም በብዙዎች የሳቱ ቢኆንም ቅሉ እውነተኛ ክርሰቲያኖች ግን ራሳችንን ከዓለም ነውር መጠበቅ አለብን፡፡

2- ዕለት ዕለት ራሳችንን በእግ ዚአብሔር ፊት ማቅረብ ደግሞ ሌላው ጉዳይ ነው፡፡ የእግዚአብሄር ቃል ሳታቁዋርጡ ዘውትር ጸልዩ ይላልና ፤   1ተሰሎንቄ 5፤16፤ ይህም እየተገለጠ ባለ ስህተት እንዳንወሰድ ይጠብቀናል፡፡ከዚሁ ጋር በንስሀ ፊቱ መውደቅና በፍጹም መንፈሳዊነት ህይወታችንን ጠብቀን መኖር አስፈላጊ ነው፡፡

3-ለጠፉ ወንድሞቻችን እና እህቶ ቻችን ወንጌልን መመስከርም ሌላው የቤት ስራችን ነው፡፡ሰው አንድ ጊዜ ከሞተ ሌላ የንስሀ ዕድል አይኖረውም ፤ወገኖቻችን ለዘላለም ወደሚፈረድበት እና ዳግመኛ ዕድል ወደ ሌለበት ቦታ ከመሄዳቸው በፊት ዓለምን ሊያድን ከመጣው ክርስቶስ ጋር መታረቅ አለባቸው፤ሐጢያታቸውም በክርስቶስ ደም መታጠብ አለበት፡በሐጢያታችን ምትክ ሆኖ ተሰቅሎ የሞተውን በሶስተኛውም ቀን የተነሳውን በ40ኛው ቀንም ወደ ሰማይ ያረገውን ክርስቶስን ማመን እንዲችሉ ልንረዳቸው ይገባል፡፡

ክርስቶስ በቅርብ  ዳግም ወደ ዓለም ይመጣል ያን ጊዜም የዓለም መጨረሻው ይሆናል፡፡ ነቅተን እንድንጠብቀው ጌታ ይርዳን፡፡

                                                                                                 benjabef@gmail.com

No comments:

Post a Comment