Friday, January 2, 2015

የጌታችን ልደት /ገና/

                                 የክርስቶስ  ልደት   /ገና/

አስቀድሜ እንኩዋን ለጌታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ ልደት በዐል በሰላም አደረሳችሁ እላለሁ፡፡

      ''እነሆ ለህዝቡ ሁሉ የሚሆን ታላቅ ደስታ የምስራች      እነግራችሁዋለሁና አትፍሩ ዛሬ በዳዊት  ከተማ  መድሐሀኒት  እርሱም  ክርስቶስ  ጌታ  የሆነ ተወልዶላችኃልና.....''ሉቃ.2፤11

የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ መወለድ ለሰው ልጆች ሁሉ መልካም ዜና ነው፡፡እርሱ የዓለምን ሁሉኀጢይት ለማስወገድ ተወለደ፡፡መለዐኩ ቅዱስ ገብርኤል ለቅድስት ማርያም እንዳበሰረው ''....ስሙን  ኢየሱስ ትዬዋለሽ እርሱም  ታላቅ ይሆናል የልዑል ልጅም ይባላል.." የሉቃስ ወንጌል ምዕራፍ 2 ቀ. 32  ፡፡

ምናልባት ብዙ ጊዜ በተለምዶ ብቻ ገናን ማክበር እየተስፋፋ የሄደ ጉዳይ ነው፡፡ ፈረንጆቹ  በልደቱ  ቀን ስጦታን መለዋወጠ፤ዛፎችን በደመቀ መብራት ማሸብረቅ፤መብላት እና መጠጣት የመሳሰሉትን ጉዳዮች በመፈጸም ቀኑን ያሳልፋሉ፡፡ከበዛ ደግሞ ሳንታ ክሎስ ብለው ከሰየሙት የገና አባት ጋር ፎቶ መነሳት ህጻናቶችን  ማስደሰት....የመሳሰሉትን ያደርጋሉ፡፡እንደውም አሁን አሁን ገና ማለት የልጆች ጊዜ ለማድረግ ትንሽ የቀረው ይመስላል፡፡ይህ ማለት ከዋናው ጉዳይ ጋር እየተለያየን ነው ማለት ነው፡፡

በአገራችንም ከዚህ ባልተናነሰ ሁኔታ ባህላዊ ምግቦችን በማዘጋጀት እና የገና ዛፎችን በማስጌጥ ሲዘፈን ሲጨፈር መዋል የተለመደ ነገር ሆኑዋል፡፡ብቻ በሁሉም ጎን ማለት ይቻላል ፈር የለቀቀ ጉዳይ ይስተዋላል፡፡ማለትም ከዋናው ጉዳይ ጋር ያለተገናኙ ነገሮች የበዐሉ ዋና ነገር ሆነው ቀርበዋልና፡፡

ከርስቶስን  ከውልደቱ ጀምሮ ሊገድለው ሲፈልግ የነበረ ሰይጣን፤ በሁዋላም ከሞት መነሳቱን በውሸት ዜና ተክቶ አልተነሳም ብለው እንዲናገሩ ሲጥር የነበረው ሰይጣን፤ አሁን ደግሞ ስልቱን ቀይሮ ሰዎች የገናን ትክክለኛ ነገር እንዳይረዱ በማድረግ በሚችለው ሁሉ እየሰራ ይገኛል፡፡በተወሰነ መልኩ የተሳካለትም ይመስላል፡፡

የልደቱን ባለቤት በቅጡ ያልተረዳ ህዝብ ገናን ቢያከብር ለሰይጣን የራስ ምታት አይደለም ፡፡ ብዙዎች ክርስቶስን ለሌላ ሀይማኖት እየሰጡ: ከልብና ከቤት አስወጥቶ  ፤ደግሞ  ሌሎች ምናልባት ያልተቀበሉትን የኢየሱስን ልደት ለማክበር ደፋ ቀና ማለት ምን ያህል ያለማስተዋል ይሆን ? ምዕመናን  ሆይ  ልብ ልንል የሚገባው ዋና ነገር የተወለደው ክርስቶስ በእኛ ልብ ስለመኖሩ እና የተወለደበት፣የተሰቀለበት፣የሞተበትንና፣የተነሳበት ትክክለኛ ዓላማ ገብቶናል ወይ የሚለው ቁም ነገር ነው፡፡


ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እኛን ከሐጢያት ለማዳን ተወለደ፤በእርሱ የሐጢያታችንን ስርየት እናገኛለን /የሐዋርያት ሥራ.10፤43/፤ መጽሐፍ በእርሱ የሚያምን ሁሉ አያፍርም ይላል፡፡ ሮሜ 10፤11

እርሱ  የህይወታችንም  የክርስትናችንም መሰረት ነው፡፡ ያውም በልደቱ  ቀን እርሱን ደስ የማያሰኘውን ጉዳይ  እየፈጸምን እርሱን አስወጥተን ወይም ቸል ብለን ድግሱ ላይ ብቻ የምናተኩር ከሆንን ምኑ ላይ ነው ክርስትናው?  ያስብላል፤

እህቶቼና ወንድሞቼ አባቶቼና እናቶቼ ምንም እንኩዋ ብዙ ዓመታት ሳይገባን ያደረግን ቢሆን አሁን ግን ወደ እውነት እንመለስና ትክክለኛውን ልደት እናክብር ንስሐ እንግባ፣በደሙም ፊቱ በመቅረብ እንቀደስ፡፡

ልብዎ ፈቃደኛ  ከሆነ ቀጥሎ ያለውን ጸሎት ይጸልዩ፡-እግዚአብሄር ሆይ አንድያ ልጅህን ወደ ዓለም ልከህ ስለ እኔና ስለ ዓለም ሐጢያት እንዲወለድ ስላደረግህ አመሰግንሀለሁ፡ከልጅነት እስከ ዕውቀት የሰራሁትን መተላለፍና ሐጢያት ይቅር በለኝ፡፡ጌታ  ሆይ ወደ ልቤ እንድትገባ እፈቅድልሀለሁ ሁለጊዜ አንተን በማመን ጸንቼ እንድኖር እርዳኝ በጌታችን በመድሀኒታችን በኢየሱስ ክርሰቶስ ስም አሜን፡፡

                                                                                                             benjabef@gmail.com

1 comment: