Sunday, May 17, 2015

ስለ ታቦት ሚስጥር...

        በስመ አብ ፡ ወወልድ፡ ወመንፈስ ቅዱስ አሀዱ አምላክ አሜን፡፡
      በዛሬው ርዕስ ውስጥ ቀጥሎ የምትመለከቱትን ቪዲዮ ሰሞኑን ከዩቱዩብ ላይ አግኝቼ ልቤ በጣም ስለተነካ ፡ትምህርቱን ሁሉም ሰው ቢሰማው ይጠቀማል ብዬ አሰብኩ፡፡ እንደነዚህ የሆኑ የክርስቶስን ክቡር ወንጌል ለህዝቡ የሚናገሩ የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ካህናትና አባቶች  ስላሉ እግዚአብሔር የተመሰገነ ይሁን፡፡ የቤተክርስቲያን ራስ እና ጌታ የሆነው ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለህዝቡ ና ለቤተክርስቲያኑዋ አሁንም በጎ ሐሳብ እንዳለው ያሳያል፡፡ አባታችን ያስተማሩትን ይህንን ትምህርት ሰምተን መለወጥ ይሁንልን፡፡ እግዚአብሔር ለሁላችን ልቦናን ይስጠን፡፡ አሜን!

አስተያየት፡- ስለ ታቦት በተሰጠ ሶስተኛው ትርጉም ወይም ትንታኔ ላይ ብዙዎች የተለየ ሐሳብ አላቸው፡፡ ይኸውም በኢትዮጵያ አብያተ ክርስቲያናት የሚገኙ ታቦታት ሁሉ በአብዛኛው ስያሜያቸው በጌታችን በመድሐኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ባለመሆኑና  በምትኩ  በሌሎች ሰማዕታትና መላዕክት ስም የተሰየመ በመሆኑ ‹ጉልበት ሁሉ ለስሙ /ለጌታ ለኢየሱስ ክርስቶስ / ይንበረከካል› ፊሊ.2 ቁ.10 ከሚለው አውነተኛ ቃል ጋር የሚጋጭ ነው፡፡በመሆኑም በአዲስ ኪዳን ዘመን ለምሳሌነት የተቀመጠ እና በሰው እጅ ለተቀረጸ  ነገር መገድ ተገቢ  አይደለም ይላሉ፡፡

ማስታወሻ ፡- ለወገኖቻችን፣ ለወዳጅ -ዘመዶቻችን ሁሉ ሼር በማድረግ  የወንጌልን እውነት አብረን እንድናሰማ  እጠይቃለሁ!!

                                                                                                                    benjabef@gmail.com


No comments:

Post a Comment