Monday, June 8, 2015

የመኖሪያ ቤት ምዝገባ !

‹‹ ልባችሁ አይታወክ ፤በእግዚአብሔር እመኑ፡ በእኔም ደግሞ እመኑ፡፡ በአባቴ ቤት ብዙ መኖሪያ አለ፡፡ እንዲህስ ባይሆን ባልኩዋችሁ ነበር ስፍራ አዘጋጅላችሁ ዘንድ እሄዳለሁና፡፡ ሄጄም ስፍራ ባዘጋጅላችሁ እኔ ባለሁበት እናንተ ደግሞ እንድትሆኑ ሁለተኛ እመጣለሁ፡ ወደ እኔም እወስዳችሁዋለሁ፡፡›› ዮሐ.14፡1-3

በስማችን የተመዘገበ የምድራዊ መኖሪያ ቤት ሊኖረንም ላይኖረንም ይችላል፡፡ ቢኖረንም በጣም ጥቂት ጊዜ የምንኖርበት ነው፡፡ እኛም ቢሆን ቤቱ ያልፋሉና፡፡ ትልቁ ጉዳይ በዘላለም ቤት በመንግስተ ሰማይ ቤት የሌለን እንደሆነ ነው፡፡

       ለዘላለም ቤት እንዲኖርዎ ምን ማድረግ አለብዎ?

1. የዘላለም መንገድ ፣እውነት እና ህይወት በሆነው በኢየሱስ ክርስቶስ ማመን!
   ቃሉ እርሱን ክርስቶስን ብንክደው እርሱም ይክደናል ይላል፡፡ 2 ጢሞ.2፡12

2. ከሐጢያትዎ ሁሉ በንስሐ ተመልሰው ፡ መልካም ፍሬን ማፍራት፡፡

3. በቀሪ ዘመንዎ በፍጹም ልብ ክርስቶስን ለመከተል መወሰን፡፡ ይህን ሲያደርጉ ህይወትዎ ይለወጣል፤ የዘላለም ቤትም በሰማይ ይዘጋጅልዎታል፡፡

ማስታወሻ፡-ይህንን መልዕክት ለሌሎች ሼር ያድርጉ! 
/በተጨማሪ ለማንበብ ይህንን ይጫኑ http://tehadesothought.blogspot.com  

No comments:

Post a Comment