Tuesday, June 16, 2015

ፀሎተ ሐይማኖት !

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ  ተዋህዶ ቤተክርስቲያን የሐይማኖት ጸሎት! በኒቂያ ጉባኤ በ 325 ዓ.ም. የተደነገገ፡፡

ሁሉን በሚገዛ ሰማይንና ምድርን የሚታየውንና የማይታየውን በፈጠረ በእንድ አምላክ በሚሆን በእግዚአብሔር አብ እናምናለን፡፡

      ዓለም ሳይፈጠር የአብ አንድ ልጁ በሚሆን በአንድ ጌታ በኢየሱስ ክርስቶስ እናምናለን፡፡ እርሱም ከብርሐን የተገኘ ብርሐን ከእውነተኛ አምላክ የተገኘ አምላክ የሚሆን : የተፈጠረ ያይደል የተወለደ : በመለኮቱ ከአብ ጋር አንድ የሆነ ሁሉ በእርሱ የሆነ : በሰማይና በምድር ካለው ሁሉ ያለ እርሱ ምንም የሆነ የሌለ : ስለ እኛ ስለ ሰዎች እኛንም ስለማዳን ከሰማይ ወረደ : በመንፈስ ቅዱስም ከቅድስት ድንግል ማርያም ስጋን ለበሰ: ሰውም ሆነ በጴንጤናዊው በጲላጦስ ዘመን ስለ እኛ ተሰቀለ: መከራን ተቀበለ ሞተ ተቀበረም በቅዱሳት መጻሕፍት እንደተጻፈ በሶስተኛው ቀን ከሙታን ተለይቶ ተነሳ በክብርም ወደ ሰማይ ዐረገ በአባቱም ቀኝ ተቀመጠ ዳግመኛም በሕያዋንና በሙታን ይፈርድ ዘንድ በጌትነት ይመጣል ለመንግስቱም ፍጻሜ የለውም፡፡

     ከአብና ከወልድ ጋር በአንድነት በሚሰገድለትና በሚመሰገን ጌታ ሕይወት ሰጭ በሚሆን ከአብ በሠረፀ በነቢያትም በተነገረ በመንፈስ ቅዱስ እናምናለን፡፡ በሁሉም ዘንድ በምትሆን ሐዋርያት በሰበሰቡአት በአንዲት ቅድስት ቤተክርስቲያን እናምናለን፡፡ ለኃጢአትም ስርየት : በአንዲት ጥምቀት እናምናለን፡፡ የሙታን ትንሳኤንና የሚመጣውን ዓለም ሕይወት በተስፋ እንጠባበቃለን፡፡ አሜን፡፡


     እንግዲህ የኢትዮጵያ ኦርቶድካሳዊት ቤተክርስቲያንም የተቀበለችው እውነት ይህ በመሆኑ ምዕመናን ሁሉ እንዲረዱት ፣እንዲያጠኑት ማገዝ ይጠበቅብናል፡፡ ስለ እኛ የተሰቀለውንና የሞተውን ደግሞ ከሙታን ተለይቶ የተነሳውን ጌታ ባለማመንና ባለማወቅ ሲኦል እንዳይገቡ ሁላችን የምንችለውን ሁሉ ስለ ወንጌል እናድርግ !!!

ተጨማሪ ንባብ ከፈለጉ እዚህ ይጫኑ http://tehadesothought.blogspot.com


 እግዚአብሔር በነገር ሁሉ ታማኝ አምላክ ነው ! ይህችን መዝሙር ተጋበዙ...

No comments:

Post a Comment