Saturday, June 6, 2015

ክፍት የስራ ቦታ!

 እግዚአብሔር ለሰው ሁሉ የፈቀደው ስራ ምንድን ነው? መጽሐፍ ቅዱስ እንዲህ ይላል፡-

''...ይህ የእግዚአብሔር ስራ እርሱ  በላከው  እንድታምኑ ነው፡ ...፡፡ '' ዮሐ.6፡29

'' እርሱ ''-የተባለው ሁሉን የፈጠረ አምላካችን እግዚአብሔር አብ ሲሆን  '' የተላከውም '' አንድያ ልጁ ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርሰቶስ ነው፡፡

የእኛ ድርሻ፡- በአባቱ ተልኮ ወደ ምድር በመምጣት፣ በቅድስት ድንግል ማርያም ማህጸን ተወልዶ፣ ተሰቅሎ ፣ ለሐጢያታችን ስርየት እንዲሆን ክቡር ደሙን አፍስሶ፣ ሞቶ፣ በሶስተኛው ቀን ተነስቶ ደግሞ በ 40ኛው ቀን ያረገውን ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን ማመን ነው፡፡

 ልብ ይበሉ ለእርስዎ የተዘጋጀልዎ የእግዚአብሔር ስራ በልጁ በክርስቶስ ማመን ነው ! በእርሱም የሚያምን መጽሐፍ እንደሚል የዘላለም ህይወትን ያገኛል ዮሐ.3፡16 ፡፡ ለምድራዊ ኑሮዎ ግን ምድራዊ ስራ መስራት ሐጢያት አይደለም፡፡

ለተጨማሪ ትምህርት ይህንን ይጫኑ  http://tehadesothought.blogspot.com

No comments:

Post a Comment