Saturday, June 6, 2015

ለቪዛ ፈላጊዎች !

የተለያዩ ሰዎች ኑሮአቸውን ለማሻሻልና ለማሸነፍ  በርካታ መንገዶችን ተጠቅመው ከአገር ይወጣሉ፡፡ አንዳንዱ ህጋዊነትን ተከትሎ የሚፈጸም ሲሆን፡ በተቃራኒው ህጋዊነትን ባልተከተለ መንገድ ለብዙ እንግልትና ስቃይ እየተዳረጉ አገር የሚቀይሩም ዜጎች አሉ፡፡ ይህም በዋነኝነት ሁሉም ሰው የሚፈልገውን  የቪዛ ጥያቄ እንደሚፈልገው ስለ ማይፈቀድለት እንደሆነ ይታወቃል፡፡ ቪዛ  የሚፈቀድበት የራሱ መስፈርትና አሰራር አለው፡፡

   ይህ ሲባል ግን ትክክለኛ ቪዛ ያገኙ ሰዎች የሚሄዱበት ምድር ችግር አይገጥማቸውም ማለት አይደለም፡፡ እዚሁ ዓለም እስከሆነ ድረስ የትም አገር ቢሆን የራሱ የሆነ አሉታዊ ተጽዕኖ አለው፡፡ አንደየ ቦታው ሁኔታ ግን ሊለያይ ይችላል፡፡

በእርግጠኝነት ቪዛ ሊያገኙበት የሚችሉበት፣ በሚሄዱበት አገርም ምንም አይነት ችግር የማይገጥሞዎት አንድ አገር ብቻ ነው፡፡ይህን ዕድል ለመጠቀም ከፈለጉ በጥንቃቄ ቀጣዩን መስፈርቶች ይከታተሉ፡፡

መጽሐፍ ሲናገር  ''...ቅድስቲቱ ከተማ አዲሲቱ ኢየሩሳሌም ለባልዋ እንደተሸለመች ሙሽራ ተዘጋጅታ ከሰማይ ከእግዚአብሔር ዘንድ ስትወርድ አየሁ፤....ሞት ከእንግዲህ አይሆንም ፡ኀዘንም ወይም ጩኸት ወይም ስቃይ ከእንግዲህ ወዲህ አይሆንም፡፡'' ራዕይ 21፡1-4፡፡ በዚህ አዲስ አገር ውስጥ ምንም ችግርና ሰቆቃ የሌለ ሲሆን ደስ በሚል ብርሐን ውስጥ ሰላምና ዕረፍት አግኝቶ ከዘላለም እሰከ ዘላለም ድረስ መኖር ያስችላል፡፡

ቪዛውን ታዲያ እንዴት ማግኘት ይቻላል?

የዮሐንስ ወንጌል ምዕራፍ 3 ቁ.16-21 ያንብቡ፡፡ በጌታችንና በመድኀኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ይመኑ! እርሱም ስለ እኛ ሐጢያት የተሰቀለ፣ የሞተ፣ በሶስተኛውም ቀን የተነሳ ነው፡፡ ልክ  ስለ  እርሶ የሞተውንና  የተነሳውን  ክርስቶስን  አምነው  ንስሐ  ሲገቡ ፡ ስምዎ  በህይወት  መጽሐፍ  ላይ ይጻፋል፤  የመንግሰተ  ሰማይ  መግቢያ  ቪዛውን ም ይቀበላሉ፡፡

       ለጥንቃቄ
  • ይጠንቀቁ! ቪዛውን እኛ እንሰጣለን የሚሉ ክርስቶስ የማያውቃቸው ና ህጋዊውን መንገድ የማይከተሉ በርካታ ሐይማኖታዊ ድርጅቶችና አገልጋዮች አሉ፡፡ መንገዱ አንድ ብቻ ነው እርሱም ክርስቶስ ነው፡፡ ዮሐ 14 ቁ.6፡
  •  ንስሐ ገብተውና ተዘጋጅተው ፣ በማመን ያገኙትን የመዳን ቪዛ ይዘው ጌታ እስኪገለጥ ድረስ በእምነት ጸንተው ይጠብቁ!
  •  ቃሉን /መጽሐፍ ቅዱስን/ ያንብቡ ፣ በየዕለቱም ይጸልዩ!
                      Click here  For more Teachings http://tehadesothought.blogspot.com                                                                                         


No comments:

Post a Comment