Tuesday, November 27, 2018

ከ 32 ዓመታት በኋላ ይፀፅትሃል??

ከ 32 ዓመታት በኋላ ይፀፅትሃል??

በቅርብ ጊዜ የአንድ ወዳጃችን 20ኛ  የሚንስትሪ
ዓመቱን ክብረ በዓል አስመልክቶ በተዘጋጀ እራት ላይ እንድንገኝ ተጠርተን ስለነበር ወደዚያው አቀናን፤ እኔም አንዱ ተካፋይ ነበርኩ። ይህ ሰው በአብዛ ኛው ዓለም ላይ ወንጌልን አስተምሯል፤ ምናልባት ከ195 በላይ የዓለም ከተሞች ላይ ፤ በኢትዮጵያ ደግሞ 60 ያህል ከተሞች ውስጥ  ተዘዋውሮ ወንጌልን ስብኳል፤ በ30 ዓመት የአገልግሎት ጊዜው በርካታ መንፈሳዊ ስራዎችን እንደሰራ፤ በሚሊዮን የሚቆጠሩትን በየሳምንቱ በሚድያ በኩል እንዳገኛቸው፤ ሺዎች በእርሱ አገልግሎት ወደ እግዚእብሔር መንግስት እንደተጨመሩ ምስክርነት ቀረበ! አቤት ደስ ሲል! የሆነ ሆኖ ይኽው አይደል የሚፈለገው? ቀሪ ዘመኑንም ሲያገለግል ይለቅ ብዬ በውስጤ መረቅኩት። በዚህ ሁሉ እየተደነቅን..  ይህን ሰው ግን ማን ወደ ክርስቶስ አመጣው? እንዴትስ ጌታን አገኘ? የሚል ጥያቄ ሰው ውስጥ ያለ ይመስለኛል፤ ዝግጅቱ ከመጠናቀቁ በፊት  ለ7 ደቂቃ ንግግር እንዲያደርግ  የፕሮግራሙን  መርሃ ግብር በሚመራው ሰው ተጋብዞ ወደ መድረክ መጣ፤.. ..ከአገልግሎቱ  ጋር የተያያዘ ጥቂት ነገር ተናገረ፤ በህይወቱ ውስጥ  ጠቃሚ ሚና  የነበራቸውን ሰዎችም እልረሳቸውም ፤ ከድሮ እስከ አሁን አመሰገናቸው!...። በተለይ የእኔን ቀልብ የሳበው ደግሞ የአንድ ሰው ሁኔታ ነበር፤ ያ ሰው የዛሬ 32 ዓመት ለዚህ አንጋፋ ወንጌላዊ ለመጀመሪያ ጊዜ ወንጌል የመሰከረ ፣ እምብዛም የማይታወቅ ሰው ነበር። በእርግጥ ወ/ዊ ያሬድ ጌታን እንደ ግል አዳኝ አድርጎ ወስኖ የተቀበለው ጅቡቲ ውስጥ ነው። ከዚህ ጋር ተያይዞ ጥቂት ስለህይወቱ እንዲነግረኝ  ጠይቄው ነበር፤ ተከታዩን ምላሽ ሰጥቶኛል እነሆ:-

1.ጌታን ሳታውቅ በፊት ምን አይነት ሰው ነበርክ?
ወ/ዊ ያሬድ:-  በልጅነት ማለት እስከ 13 ዓመት
አጥባቂ የሃይማኖት ሰው ነበርኩ፤ በጊዜው ከአቡነ ኤልሳዕ (ጳጳስ የነበሩ) እጅም ድቁንናን ተቀብያለሁ፤ ከዚያ በኋላ ደግሞ በኪነ ጥበብ ውስጥ ማዘጋጃ ቤትና ብሔራዊ ቲያትር ውስጥ ትወናና የተወሰነ ግጥም ድርሰት ላይም ተሳትፌያለሁ። 

2.ጌታን የመሰከርልህ ሰው ምን ብሎ መሰከረልህ? ከዚያስ በኋላስ ምን ተፈጠረ?
ወ/ዊ ያሬድ:-በስደት ውስጥ ሆኜ በጣም ተስፋ ከመቁረጤ የተነሳ ራሴን ማጥፋት አስብ ነበር ፤
በዚህ መሀል በምኖርበት በር ላይ ዘውትር የሚያልፍ አንድ በህይወቱ ደስታ የሚነበብበት አማኝ ዘውትር ሳየው እቀናበት ስለነበረ እባክህን የዚህን ደስታ ሚስጥሩን ትነግረኝ? ብዬ ጠየኩት፤ የሰላሙንና የደስታውን ምስጢር ነገረኝ፤... ከዚያማ ያ ደስታ እኔም ውስጥ ገባ፤ "ሚስጥሩ" እኔ የጎደለኝ "ኢየሱስ ክርስቶስ" ነበረ። ኢየሱስ ክርስቶስን የህይወቴ ጌታ አደረኩት!

3.ህይወትህን የለወጡ ዋና ዋና ነገሮችን እስቲ ንገረኝ ?
ወ/ዊ ያሬድ:-በተለይ በቅዱሳን ህብረት ውስጥ ያገኘሁት ጥቅም እጅግ ነው፤ ሌላው የእግዚአብሔርን ቃል (መጽሐፍ ቅዱስን) አጠና ነበር፣..ለጸሎትም ጊዜ ነበረኝ፤ እነዚህ ነገሮች ህይወቴ የበለጠ ከጌታ ጋር እንዲጣበቅ እረድተውኛል።

4. በዳንክ ሰሞን የውስጥና የውጪ ተግዳሮቶችህ ምን ነበሩ?
ወ/ዊ ያሬድ:-እንዳልኩህ ስደት አገር ነው እኖር የነበረው፤ የአገሩ ሕዝብ ባብዛኛው እስልምናን የሚከተል በመሆኑ የማምለክ ነጻነት እምብዛም አልነበረም! በዚህ ምክንያት እስር ቤት ታስሬም አውቃለሁ...በስደት ውስጥ ነገ ምን ይፈጠር ይሆን ? የሚሉ ስጋቶች አሉ፤ እኔም ውስጥ በተወሰነ መልክ  የነበረ  ነው።

5. ከ32 ዓመት በፊት ወስነህ ጌታን በመከተልህ ዛሬ ላይ ሆነህ ይቆጭሃል? ወይስ..?
ወ/ዊ ያሬድ፡-የግርምት ሳቅ...! እንዴት ሆኖ? ዘላለሜን ስለዚያች ዕለት ስባርከው እኖራለሁ እንጂ! ሃሌ ሉያ!

6.በመጨረሻ ይህን መልዕክት ለሚያነቡ ሁሉ ምን ልታስተላልፍ ትወዳለህ?
ወ/ዊ ያሬድ፡-ሰው የሆነ ሁሉ ይህችን ምድር ነክቶ ሲያልፍ አንድ ትልቅ ውሳኔ ወስኖ እንዲያልፍ እፈልጋለሁ፤ ይህም ኢየሱስ ክርስቶስን የህይወቱ ጌታና አዳኝ እንዲያደርግ! እና በቀሪ ዘመኑ ሁሉ ክርስቶስን መስሎ እንዲኖር እመክራለሁ። ብልጫ ያለው... <<የሰው ትልቁ ውሳኔ ይህ ነው።>>
አመስግናለሁ! ጌታ ይባርክህ!
እባክዎ ወንጌልን ላልሰሙ ሰዎች ይመስክሩ! የሌሎች ወንጌል አርበኞች ታሪክ ይቀጥላል...

<<LET US BE WITNESSES FOR CHRIST>>

No comments:

Post a Comment