Sunday, November 18, 2018

ኢየሱስ የእግዚአብሔር አንድያ- ልጅ ነውን?


ኢየሱስ የእግዚአብሔር አንድያ- ልጅ ነውን?



ክርስትና እምነት ዋነኛ መሰረቱ በኢየሱስ ክርስቶስ አዳኝነት ማመንና  ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ ማንነት ጠንቅቆ ማወቅ ነው፡: ስለክርስትና እምነት የሚነሱ የስህተት ትምህርቶች በአብዛኛው የሚመነጩት፣ ክርስቶስ ማንንት ላይ ተመርኩዘው በመሆኑ ስለክርስቶስ ማወቃችን የምንሰማቸው መልእክቶች ሁሉ እንዳያስቱን የበለጠ እንድንጠነቀቅ ያደርገናል፡፡ አንዳንድ የስህተት እምነቶች የተመሠረቱት ‹‹ኢየሱስ የእግዚአብሔር ልጅ አይደለም ፣አምላክ አይደለም ፣ ፍጡር ነው›› በሚሉ አደገኛ የሆኑ አስተምህሮ ላይ ተመrekuzew ሲሆን፤ ሌሎችም በኢየሱስ  አምላክነትና ጌትነት ቢያምኑም፣ ቅሉ ‹‹ክርስቶስ አልሞተም›› ወይም ደግሞ ‹‹አልተነሳም›› በሚል ኑፋቄ ይደመድማሉ፡፡ በሌሎች የክርስትና ጉዳዮች ላይ ተመርኩዞ የተፈለሰፈ ስህተት የለም ማለት አይደለም፡፡ ይሁንና አንዳንዱ ስህተት ድነትን የማይከለክል ሊሆን ይችላል፡፡ የክርስቶስ ማንነት ላይ ተመርኩዞ የሚነሳ ስህተት ግን ድነትን እንኳ እስከማሳጣት ሊያደርስ ይችላልና መጠንቀቁ ጥሩ ነው፡፡ ሐሳውያኑ ስለ ክርስቶስ ማንነት ወይም ለድነታችን ስለ ተፈጸመው ነገር ጥቂት እውነታ ያለው ነገር ቢኖራቸውም የክርስትና ዋና ስለሆነው ኢየሱስ ክርስቶስ ግን  መሠረታዊ ነገር አጉድለው ነው የሚያስተምሩት፡፡  ብዙ ስህተቶች ከክርስትና ውጪ ሆነው፣ በስም ተሰይመው ስለሚኖሩ እነርሱን ለይቶ ማወቅ ብዙ ጊዜ አያስቸግር ይሆናል፡፡ ለምሳሌ የዮሕዋ ምስክሮች፣ ሞርሞኖች…ወዘተ ግልጽ ስህተት አንግበው የሚጓዙ እምነቶች ናቸው፡፡ የራሳችን በሆኑና በማንጠራጠራቸው ወንድሞች የሚነሱ ስህተቶች ግን ይልቁን አደገኛ ናቸው፡፡ እንደኛው የሚዘምሩ ፣እንደኛው ልሳን የሚናገሩ፣ ተመሳሳይ መጽሐፍ ቅዱስ እየተጠቀሙ ግን በተለየ አተረጓጎም፣ በተለየ አስተምህሮ የተገለጡ ናቸው፡፡ ስለዚህ ነው እንግዲህ ነገሩን የበለጠ አሳሳቢ የሚያደርገው፡፡  



  በዚህ ርዕስ ላይ እንድጽፍ ምክንያት የሆነኝ ሰሞኑን በአንድ ማኅበራዊ ገፅ (ሶሻል ሚዲያ) ላይ የተመለከትኩት መልዕክት  ነው፡፡   በማህበራዊው መገናኛ ፊት ለፊት ገጽ ላይ ‘’No more  Begotten Son” በሚል ርእስ ጽሐፍ ተጽፏል፡፡ ወደ አማርኛ ስንመልሰው ‹‹አንድያ ልጅ የሚባል ነገር ከእንግዲህ የለም›› የሚለውን አቻ ትርገም ይይዛል፡፡   ለመሆኑ ወዴት ወዴት እየሔድን ነው? ሀይ ባይ የለም? ይህንን መልእክት አንብቤ ዝም ከምል ወይም ሌላ ሰው ምልሽ እንዲሰጥ ከምጠብቅ እኔም ሐላፊነቱ ስለተሰማኝ የድርሻየን ምላሽ ለመጻፍ ተገደድኩኝ: ይህ አጭር ጽሑፍ፣ በተመሳሳይ የስህተት መንገድ  ላይ ያለውን ብዥታ ለማጥራት፣ በጣም ርቀው የሔዱትንና ርቀው ለመሄድ ዝግጅት ላይ ያሉትን ለመመለስ ይጠቅማል ብዬ አስባለሁ፡፡

ኢየሱስ የምድር አገልግሎቱን ጨርሶ ወደመስቀል ሞት ከመሔዱ በፊት ለደቀ መዛሙርቱ ሲጸልይ ‹‹እውነተኛ አምላክ የሆንክ አንተን የላከኸውንም ኢየሱስ ክርስቶስን ያውቁ ዘንድ ይህች የዘላለም ሕይወት ናት፡፡›› (ዮሐ.17፡ 3) ነበር ያለው፡፡ ስለዚህም ስለክርስቶስ ማንነት ማወቅ እና ከስህተት መጠበቅ የእውቀት ጉዳይ ብቻ ሳይሆን ለዘላለም ሕይወት መብቃት ወይም መጉደል ያለበት ወሳኝ አቋም ነው፡፡

ስለ ክርስቶስ ማንነት ማወቅ ወይም ራሱን ክርስቶስን ማወቅ ከዕውቀት የዘለለ ትርጉም አለውየዘላለም ሕይወትም ጭምር ነው፡፡ ለዚህም ነው ጌታ  ደቀ መዛሙርቱን ‹‹የሰውን ልጅ ማን ይሉታል?›› ብሎ  ጥያቄ የጠየቃቸው፡፡ በጊዜው የነበሩት የሕብረተሰብ ክፍሎች   ስለክርስቶስ የነበራቸው መረዳት ሙሉ ስላልነበረ፣ ደቀመዛሙርቱም  ‹‹ኤርሜያስ ፣ኤልያስ፣ ከነብያት አንዱ›› የሚል መልስ ነበር የሰጡት ፡፡ ጌታም ደቀመዛሙርቱን ‹‹እናንተስ እኔ ማን እንደሆንኩ ትላላችሁ?›› ብሎ ጠየቃቸው፡፡ ጴጥሮስ ሲመልስ ‹‹ አንተ ክርስቶስ የሕያው የእግዚአብሔር ልጅ ነህ›› አለ፡፡››  ክርስቶስ የሚለው የግሪኩ ስሙ ትርጉም  በዕብራይስጥ መሲህ ማለት ሲሆን ትርጉሙም   ‹‹የተቀባ›› የሚለውን በእግዚአብሔር የተመረጠና የተላከ መሆኑን ያመለክታል ፡፡ ኢየሱስ በጴጥሮስ መልስ ከመደነቅ ይልቅ ይህንን ታላቅ እውነት የገለጠለት ላይ ነው ያተኮረው፡፡ ‹‹አባቴ እንጂ ስጋና ደም አልገለጠልህምና ብጹህ ነህ››  አለው፡፡ (ማቴ.16 ቁ.24)፡፡ ይህ ማለት የክርስቶስን ማንነት ሰው በራሱ ዕውቀት ሊደርስበት አንደማይችል ያሳያል፡፡ እግዚአብሔር ግን ስለ ራሱ ልጅ መሰከረ፡፡ እግዚአብሔር አብ እንዲህ ያለ ተመሳሳይ ምስክርነቶች በተለያየ ቦታ ስለ ልጁ መስክሯል፡፡ ለምሳሌ መጥምቁ ዮሐንስ በዮርዳኖስ ወንዝ ውስጥ ኢየሱስን ባጠመቀው ወቅት ‹‹የምወደው ልጄ ይህ ነው›› ብሎ መስክሯል፡፡ ከዚህ ጋር ተመሳሳይ በመሆነ መልኩ፣  ከሦስት ዓመታት በኋላም በደብረዘይት ተራራ ከገናናው ክብሩ ድምጽ ወጥቶ ‹‹የምወደው ልጄ እርሱ ነውና እርሱን ስሙት›› እንዳለ ሐዋርያቱ መስክረዋል፡፡(ማቴ.17፡1-8 እና 2ጴጥ.1፡17)፡፡

 ክርስቶስ የእግዚአብሔር አንድያ ልጅ /Begotten-Son/

ኢየሱስ ክርስቶስ የእግዚአብሔር አንድያ ልጅ ነው ስንል ምን ማለታችን ነው? ‹አንድያ-ልጅ› የሚለው ቃል በእንግሊዝኛ ‹‹Only-Begotten›› በግሪኩ ደግሞ ‹‹monogeneis›› የሚባል ትርጉም አለው፡፡ ቃሉ ግን  ዳግመኛ ለተወለዱ አማኞች ሁሉ የእግዚአብሔር ልጆች ናቸው ተብሎ የተገለጸው ዓይነት ተመሳሳይ ትርጉም የያዘ ሳይሆን  የእግዚአብሔር የባህሪ ልጁ አንድ ብቻ በመሆኑ  የተለየ ማንነት ላለው የሚሰየም የተለየ መግለጫ ነው፡፡ ለምሳሌ ዮሐ.1፡14 ፣ 4፡18 ፣ 3፡16 እና 18 it would litrally mean the <only generated one.> This is the key Expression for the doctrine of <the eternal generation of the Son,> ማለትም እርሱ ክርስቶስ ሰው ሆኖ ሳይወለድ በፊትም የእግዚአብሔር አንድያ ልጅ እንደነበረ የሚያሳይ ትርጉም ነው፡፡ ቃሉ በፍጹም ሰው ሆኖ ሲወለድ ወይም ሲጠመቅ ስላገኘው የእግዚአብሔር ልጅነት የሚያሳይ አይደለም( አንዳንዶች ክርስቶስ የእግዚአብሔር ልጅ የሆነው በተጠመቀ ጊዜ ነው ስለሚሉ ነው፡፡) ይልቁንም ክርስቶስ ከዘላለም ዘመናትም በፊትም የእግዚአብሔር አንድያ ልጅ እንደሆነ ያሳያል፡፡ <beget> የሚለው ቃል <make> እና <create> ከሚባሉ ቃላት ትርጉሞች በተለየ የሚታይ ነው፡፡ ምክንያቱም ሁለቱ ቃላት ባህርይን ስለማካፈል የሚጠቀሱ አይደሉም you can only beget a child has the same nature as you have-a son or a daughter .There is nothing else you can beget (unless you were speaking very figuratively). ወንድ ልጅ ወይም ሴት ልጅ ከወላጆቻቸው ስለሚወርሱት ዘረ-መል‹Gene› ስናስብ አጠቃላ ሂደቱን <create> or <make> የሚል ቃል ልንጠቀም እንችላለን፡፡ But when you use <beget> it only means you produce a child that has your nature. ክርስቶስ የእግዚአብሔር ልጅ ነው ስንል ሙሉ ለሙሉ የመለኮትን ባህሪ ከአባቱ ተካፍሏል! ስለሆነም ኢየሱስ የእግዚአብሔር አንድያ ልጅ ስለሆነ መለኮት ነው፡፡ ዘለዓለማዊ አምላክ ነው፡፡ ሊቃውንቱ ‹የተፈጠረ ያይደል የተወለደ› Jesus was ‹begotten› not ‹made› የሚሉት ስለዚህ ነው፡፡ ከአብ ጋር አንድ ነው፡፡ (ዮሐ.10፡30).

አማኞችም የእግዚአብሔር ልጆች ተብለን ተጠርተናል፡፡ ይሁንና የእግዚአብሔር አንድያ ልጅ ግን አይደለንም፡፡ Jesus is the <Only-Begotten Son> but we are the <children of God.> ልጅነታችንንም ያገኘነው በአንድ ልጁ በኢየሱስ ክርስቶስ ባመንን ጊዜ በጸጋው የተሰጠን ችሮታ ነው፡፡(ዮሐ.1፡12-13)፡፡ በእርግጥ ከመለኮታዊ ብህሪውም ተካፍለናል ይህም በጸጋው ነው፡፡ ይህ ማለት ግን የስላሴ አካል ልንሆን፣ ምንም የማይሳነን አምላክና ፈጣሪ ተደርገናል ማለት አይደለም፡፡‹‹ ወይም ሰማዩን አርሱ ይዞ ምድር ደግሞ ያለ እኛ ፍቃድ አንድዬ ቢሆን ፍቃድ ካላገኘ መስራት አይችልም ብለው ለእግዚአብሔር ፍቃድ ሊሰጡና ሊነሱ እየፎከሩ እንዳሉ ምስኪኖችም አይደለም፡፡›› The Attributes of God ተብለው ከሚታወቁት እግዚአብሔርን ልዩ የሚያደርጉት ባህርያት He is Omniscience /ሁሉን ነገር ማወቁ/,He is Omnipresent /በሁሉም ስፍራ በአንድ ጊዜ መገኘቱ/,He is Omnipotent/ ሁሉን መቻሉ/ God. ብታስቡትስ ከቶ ሰው ይህን መሆን ይችላልን? ይህንንስ ባህሪ ከመለኮት ተካፍያለው ብሎ መናገር የሚችል ሰው አለን? ትዕቢትና ድፍረት ካልሆነ በቀር መጽሐፍ ቅዱስ ይህን አያስተምርም፡፡ እግዚአብሔር ጋር የሚገኙ የፍቅር፣የርህራሔ፣የሰላም ፣የቸርነት …ወዘተ ተቋዳሾች ግን ሆነናል፡፡ የእርሱ የጸጋው ልጆች ከተደረግን ቀን ጀምሮ ውስጣችን፣አስተሳሰባችን ተቀይሯል፡፡ ያለ ባህሪያችን ጸድቅ መባሉስ! ቅዱስ መባሉስ…ከቅድስናው በመካፈላችንም አይደል? ሌሎችን ታረቁ ማለት፣ መታገስ ፣ርህራሄ ከመለኮት ወርሰናል፡፡ብህሪውን በክርስቶስ ያካፈለን ዘላለማዊ አባታችን፣ፈጣሪያችን፣ ጌታችን ሆኖ ለዘላለም ይኖራል፡፡ እኛም እርሱን እናመልካለን ፣ እንገዛለታለን፣ እንሰግድለታለንም፡፡ ልጆች ስለተደረግን ስግደት አንተውም! አምልኮ አንተውም! እኛ ፍጡር ነን! እርሱ ፈጣሪያችን ነው፡፡ እርሱ መለኮት ነው እኛ ሰዎች ነን! ከዚህ በላይ አልፎ መንጠራራት ምንጩ ሌላ ነው! ምናልባትም ከአሳቹ ከዲያቢሎስ ነው እርሱ ቀድሞ ሕይዋንን ከዚህ ፍሬ እንዳትበሉ እግዚአብሔር የከለከላችሁ እንደ እርሱ መልካምንና ክፉን የምታውቁ እንዳትሆኑ ፈልጎ ነው ብሎ በተንኮል እንዳሳታት ተጽፏል፤ ስለዚህም እግዚአብሔር በምጸታዊ ‹‹ አዳም መልካምንና ክፉን ለማወቅ ከእኛ እንደ አንዱ ሆነ›› ብሎ ተናግሯል፡፡( ዘፍ.3፡5፣ ቁ.22)፡ ከተጻፈው ባንልፍ መልካም ነው!

መጽሐፍ ቅዱሳዊ ማስረጃዎች ስለ ዘለዓለማዊ ልጅነቱ

 ከላይ እንደተብራራው ኢየሱስ በመለኮትነቱ የእግዚአብሔር ልጅ ነው፡፡ በሰውነቱም ደግሞ በጸጋው ልጅነትን ለተቀበልን አማኞች በኩር በመሆን ልጅ ተብሎ ተጠርቷል፡፡ በሁለቱም ባሕርይው የእግዚአብሔር ልጅ እንደሆነ በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በርካታ ቦታ ተጠቅሷል፡፡

ለምሳሌ ዮሐ.5፡20 የእግዚአብሔር ልጅ በስጋ መጣ ይላል እንጂ የእግዚአብሔር ልጅ ሆነ አይልም፡፡ የዕብራውያን መጽሐፍ ጸሐፊም ይህንኑ ሲያረጋግጥ በመጨረሻ ‹ዓለማትን በፈጠረበት በልጁ ለእኛ ተናገረን፡፡› (ዕብ.1፡1-3)፡፡ ልጅነቱ ዓለማት በተፈጠሩበት ጊዜም እንደነበረ ያሳያል፡፡ ምናልባት የምሳሌ ምዕራፍ 8 አሳብና ቆላ.1፡15-18 ስለ ክርስቶስ የተነገረና አስቀድሞ ከአብ በመወለድ ፍጥረታትን ሁሉ ከአባቱ ጋር ሆኖ የፈጠረ መሆኑን ብዙዎች ይስማማሉ፡፡

ወልድ ቅድመ ዓለም የአብ ልጅ ነው፡፡ በሰው ስርዓትና አስተሳሰብ እንዴት ወለደው? መቼ ወለደው? ለሚለው መልስ ልናገኝ አንችልም፡፡ በዚህች ትንሽ አዕምሮ የሚገባን ነገርም አይመስለኝም፡፡ የምሳሌና የቆላስያሱ ጥቅሶች ግን ምንም ነገር ከመፈጠሩ በፊት እንደተወለደ እና ዓለማትን በሙሉ በእርሱ እንደፈጠረ ፍንጭ ይሰጣል፡፡(ምሳ.8፡25)፡፡ የዮሐንስ ወንጌል ም.1፡1-3 ደግሞ ‹ቃል› (ወልድ) በእግዚአብሔር ዘንድ እንደነበረ፤ ቃልም እግዚአብሔር እነደነበረ ይገልጻል፡፡›› ስለዚህ ሳይወለድ እግዚአብሔር ዘንድ የነበረ ወይም እግዚአብሔር ውስጥ የነበረ ነው፡፡ እግዚአብሔር የማታይ አምላክ ስለሆነ‹ መንፈስ ስለሆነ ‹ዓለም ሳይፈጠር በፊት እኔ ተወለድሁ› የሚለውን ቃል ይዘን እንዴት አድርጎ ወለደው; ብለን መጠየቅ የለብንም፡፡ሰማያዊ ፣መለኮታዊ ድርጊት ነው፡፡ ዋናው ነገር ወልድ ከአብ እኩል የነበረ‹ያለ እና የሚኖር አልፋና ኦሜጋ ነው /ራዕ.22፡13/ የሚለውን እውነት መረዳት ብቻ ያስፈልጋል፡፡ ቅድመ ዓለም ከአብ የተወለደ እንጂ የተፈጠረ አይደለምና፡፡ ጳውሎስ ለፊሊስዩስ አማኞች እንደጻፈው ክርስቶስ በእግዚአብሔር መልክ ይኖር ነበር፡፡(ፊሊ.2፡7)፡፡

አይሁድ ኢየሱስን ሊገድሉት ከሚፈልጉበት ምክንያት ዋናው ደፍሮ ‹እግዚአብሔር አባቴ ነው! ››(ዮሐ.5፡18) ስላለ ነበር፡፡ እንደሚታወቀው ኤሁድ እራሳቸው ራሳቸውን የእግዚአብሐሔር ልጅ አድርገው የመቁጠር ልማድ እንዳላቸው በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ተጠቅሷል፡፡ በዮሐ.8 ቁ.41 ላይ ‹‹..አንድ አባት አለን እርሱም እግዚአብሄር ነው››ብለው ተናግረዋል፡፡ ክርስቶስ የእግዚአብሔር ልጅ ነኝ ሲል ግን ይቆጡ ነበረ፡፡ ለምነ; ምክንያቱም እርሱ የእግዚአብሔር ልጅ ነኝ ሚልበት መንፈስ ገብቷቸዋል፡፡ ልጅ ነኝ ሲል መለኮት ነኝ! ፣ ፈጣሪ ነኝ! ከሁሉም በፊት ነበርኩ ራሴ እግዚአብሔር ነኝ ማለቱ ነበረ፡፡ የክርስቶስ የመከራው ሳምንት ተብሎ በሚታወቀውም ጊዜ አካባቢ ሊቀ ካህኑ ‹‹የብሩክ ልጅ ክርስቶስ አንተ ነህን?›› ብሎ ሲጠይቀው አዎ እኔ ነኝ ብሎ መልስ ሰጥቷል፡፡/ማር.14፡61/በዚያን ጊዜም ምክንያት እየፈለጉ ለነበሩ አይሁዶች እንደ አንድ ትልቅ የምስክርነት ግብዐት እንዲሆናቸው ተጠቅመውበታል፡፡ አይሁዶች በብሉይ ኪዳንም ቢሆን እግዚአብሄር አባታችን ነው ብሎ የመጥራት ችግር አልነበረባቸውም (ዘፀ.4፡22-23)፡፡ በተጨማሪ ክርስቶስ በመስቀል ላይ በሞተበት ሰዐት ከስድስት ሰዐት ጀምሮ እስከ ዘጠኝ ሰአት ድረስ በምድር ላይ ጨልሞ ነበር፡፡ ወዲያውም የመቶ አለቃው ስለ ክርስቶስ ‹‹በእውነትም የእግዚአብሔር ልጅ ነበር ››(ማር.15፡39) ብሎ መስክሯል፡፡



   እግዚእብሔር አንድያ ልጁን ነው የላከልን፡፡ ልጁ አንድ ብቻ እንደሆነ ሲገልጥ ‹አንድ ልጅ በአባቱ ዘንድ እንዳለው …ክብሩን አየን› (ዮሐ.1 ቁ.14)፡፡ ቃሉ ‹‹ለገዛ ልጁ ያልራራለት ነገር ግን ስለሁላችን አሳልፎ የሰጠው (ሮሜ.8፡32) የሚለው ቀድሞውንም ልጁን እንጂ የላከልን ለዚህ ዓላማ ሲል ቆይቶ ልጅ የተደረገ  አይደለም- የሞተልን፡፡ ይህንን በሌላ በብዙ ማስረጃ ማስረዳት ይቻላል፡፡ ለምሳሌ እግዚአብሔር ወደ ዓለም ብዙ ባርያዎቹን(አገልጋዮቹን) ልኮ ሁሉንም ስለገደሏቸው በመጨረሻ ልጄንስ ያፍሩታል ብሎ /ልጄ የሚለው አንድ ልጁ ክርስቶስን ነው/ እንደሰደደው (ማቴ…..) ተገልጧል፡፡ ዕብራውያን ምዕራፍ አንድም እግዚአብሔር ከጥንት ጀምሮ ለአባቶቻችን ሲናገር የተለያዩ መንገዶችን ተጠቅሞ እንደነበረ በመጨረሻ ግን ዓለማት በፈጠረበት በልጁ እንደተናገረን ያሳያል፡፡
May God bless you!
benjabef@gmail.com

No comments:

Post a Comment