Tuesday, November 27, 2018

ታላቁ ተልዕኮ በኢትዮጵያ


የወንጌል ሪፖርት

እግዚአብሔር ይመስገን! ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የዛሬ ሁለት ሺህ ዓመት ገደማ ስጥቶ የሄደውን አደራ በትውልድ ቅብብሎሽ ውስጥ በህብረትም ሆነ በግል እየተሰራ ግስጋሴውን ቀጥሏል።  በኢትዮጵያ ውስጥ ወንጌልን ላልሰሙ ሁሉ በማድረስ ረገድ ከፍተኛ ሥራ አየሰሩ ካሉት ተቋማት መካከል ታላቁ ተልዕኮ አገልግሎት ዋነኛው ነው። ወንድም ግርማ አልታዬ በአሁኑ ሰዓት የተቋሙ (አገልግሎቱ) ዋና ዳይሬክተር በመሆን ያስተባብራል፤ ከዚህ በፊት ጋሽ አሸናፊ ፣ ጋሽ ማስረሻ፣ ወንድም ዳምጠው ክፈለው እና ዶ'ር በቀለ ሻንቆ በተለያየ ጊዜ ይህንን ተቋም መርተዋል፤ ጌታ እንደሰጣቸው ጸጋ የተለያዩ ንድፎችን በመንደፍ ወንጌልን በኢትዮጵያ ውስጥ አሠራጭተዋል። በአሁን ሰዓት <ታላቁ ተልዕኮ በኢትዮጵያ >አዳዲስ ዕቅዶችን ይዞ በመላው ኢትዮጵያ ወንጌልን እያዳረሱ ና አዳዲስ ሕብረቶችን እያቋቋሙ ሲሆን በቅርብ ጊዜ የቀረበው ያለፈው ዓመት ሪፖርት የሚከተለውን ይመስላል፡-
    2,588,572 ወንጌል የተመሰከረላቸው።
    62,954 ሰዎች ክርስቶስን ለመከተል የወሰኑ፤
    15,901 በክትትልና በደቀመዝሙር ት/ት የተያዙ ሰዎች
     60,401 ሰዎች የረዥም ጊዜና የአጭር ጊዜ ስልጠናዎችን ወስደዋል፤
     5,636 አዳዲስ ህብረቶች ተተክለዋል። (መረጃው ከወ/ም ሀብታሙ ኪታብ ዘገባ)  

" እንግዲህ ሂዱና አህዛብን ሁሉ በአብ፣በወልድና በመንፈስ ቅዱስ ስም እያጠመቃችኋቸው ያዘዝኳችሁንም ሁሉ እንዲጠብቁ እያስተማራችኋቸው ደቀ መዛሙርት አድርጓቸው፤ እነሆም እስከ ዓለም ፍጻሜ ድረስ ሁልጊዜ ከእናንተ ጋር ነኝ። "ማቴ.28:19-20

ክብር ሁሉ ለአምላካችን ለእግዚአብሔር ይሁን! ደስ ሲል!

<<  LET US BE WITNESSES FOR CHRIST! >>

No comments:

Post a Comment