Tuesday, November 27, 2018

ኢየሱስ ..ተገለጠልኝ!

ኢየሱስ ..ተገለጠልኝ!
/የኢራንአዊው አህመድ ታሪክ/

ዕለቱ ማክሰኞ ኦክቶበር 24, 2018 ከሰዓት በኋላ፤ አንድ ቤተሰብ ለመጎብኘት በቨርጂንያ ተገኝተን ነበር፤ ደስ ብሎን ተጫወትን ፣ጸለይን፣ ቃል ተከፋፈልን...ከተጫወትናቸው ቁም ነገሮች መካከል አንዱ  ሰሞኑን እግዚአብሔር እየሰራቸው ያሉ አስገራሚ ነገሮችን ነበር ። ለምሳሌ ባለፈው ሳምንት ፡ሐሙስ ዕለት አንድ ሰው ሲጎድል ፣ሙሉ ቤተሰብ ሴትና ወንድ አያቶችን ጨምሮ አራት ያህል ስዎች በክርስቶስ ኢየሱስ አምነው ንስሐ የገቡበት ታሪክ አስገርሞናል! ነገሩ  እንዲህ ነው በዚያ ቤተሰብ ውስጥ የ2ኛ ዓመት የኮሌጅ ተማሪ የሆነች ልጃቸው መንፈስ እያሰቃያት መታመም ከጀመረች ሰነባብታለች ፤ አንዳንድ ጊዜ እናቷን እንኳ እንደ "አውሬ" እስከ ማየት ጭምር ያደረሳት ነው ...ያም ነገር ቤተሰቡን ማወክ ጀመረ፤ መፍትሔ ጠፋ! ድንገት ከጎረቤት ያለች አንድ  ክርስቲያን እህት በነገሩ ላይ እንዲጸለይ ሃሳብ ታቀርብና ይስማማሉ፤ እርሷም ከቤተክርስቲያን ሁለት አገልጋዮችን ወስዳ ጉዞ ተጀመረ፤ እቤት እንደደረሱ ታማሚዋ ወጣት ከቤት ወጥታ ሄዳለች ፤ ቢሆንም ለተቀረው ቤተሰብ ጸሎት መጸለይ ተጀመረ። ነገሩ በዚህ ሁኔታ ቀጥሎ ሳለ አንደኛው ወንድም ድንገት ሴት አያታቸው ላይ እጅ ጭኖ መጸለይ ይሰማውና.. ሲጸልይ ከእርሳቸው ሳይሆን ከልጃቸው ላይ፡ ማለትም ከወጣቷ እናት ላይ መንፈስ ጮሆ ራሱን ገልጦ ይወጣል! በነገሩ ቤተሰቡ ድንጋጤ ውስጥ ገባ፤  ግራ መጋባትም፣ መገረምም ይዟቸው ባሉበት ሰዓት አገልጋይ ወንድማችን ጌታን እንዲቀበሉ ቆሞ በብዙ ቃል ከተናገራቸው በኋላ የነበሩት ሰዎች ሁሉ ክርስቶስን ጌታና አዳኝ አድርገው ተቀብለዋል። ክብር ሁሉ ለእግዚአብሔር ይሁን!!

ይህንንና የመሳሰሉትን እያወራን ሳለ ጋባዥ ወንድማችን በዚህ 15 ቀናት ውስጥ በመስሪያ ቤቱ የገጠመውን ታላቅ ነገር አጫወተን። ነገሩ እንደዚህ ነው የስራ ባልደረባው የ70 ዓመት ኢራናዊ ሰው ናቸው፤ ክርስቲያን ነህ አይደል? ብለው ጠየቁኝ አዎን! አልኳቸው ፤ ቀጥለውም ኢየሱስን አውቀዋለሁ! አሉ፤ እርሱም <ኢሳ> ማለትዎት ነው? አይደለም! አሉ ሰውየው ፣ "ኢየሱስን" ነው፤ በተደጋጋሚ በህልሜ መጥቶ አናግሮኛል። 12ቱ ሐዋርያትን፣ሙሴና አብርሃምን እያሳየኝ የአንተ ዕድል ፈንታ እነዚህ መሐል ነው አለኝ። በተለይ ጴጥሮስ የሚለው ስም ሲጠራ ትዝ ይለኛል ። እሺ አሁን ለማንኛውም ኢየሱስን ይቀበላሉ ? ሲል ጠየቀ፤ "I already recieved Jesus Christ as a personal Savior" አሉ ! እንዴት ? ብሎ አለ፤  ይህን እርሱ ራሱ ኢየሱስ ነግሮኝ ነው ያደረኩት አሉ። ለማንኛውም አሁን ከእኔ ጋር ንስሐ ለመግባት ፍቃደኛ ነዎት? አላቸው። አዎን! አሉ "ሙስሊሙ" ኢራናዊው አህመድ... እየመራኋቸው ንስሐ ገቡ ፤ጌታንም በእኔ እጅ እንደ ገና ተቀበሉ አለ። አሁን ተከታታይ ትምህርት ልንጀምርላቸው ቀጠሮ ይዘናል።  እንደዚህ ያሉትን ሰዎች ማስተማርማ ዕድል ነው። ኢየሱስ በታላቅ ስራ ላይ ነው ! ራሱ ተገልጦ ሰዎችን እያዳነ ነው። እኛም የታዘዝነውን እንፈጽም ዘንድ እንበርታ!

"ወደ ዓለም ሁሉ ሂዱ ወንጌልንም ለፍጥረት ሁሉ ስበኩ።" /ማር.16:15 /ወንጌልን መመስከር ከዕድለኝነትም በላይ ነው!!!
(የአሌክሳንደሪያው ኤልያስ፣መጋቢ ኤልያስ፣ መሲና ትንሱ የእግዚአብሔር ስራ ይብዛላችሁ !)

<<LET US BE WITNESSES FOR CHRIST>>

No comments:

Post a Comment