Tuesday, November 27, 2018

ቤተሰቦቻችን በሪቫይቫሉ ውስጥ..!

ቤተሰቦቻችን በሪቫይቫሉ ውስጥ..!

በ ኦገስት 30/2018 ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስን እንደ ግል አዳኝ ስለተቀበሉ አባቷ አንዲት በመካከላችን ያለች እህታችን እንዲህ ስትል መስክራለች። አባቴ በጣም አክራሪ ኦርቶዶክስ ተከታይ ነው። ብሎም በአንድ ደብር ውስጥ የሰንበቴ ጸሃፊ ሆኖ ያገለግላል። ላልዳኑ ቤተሰቦቼ ሸክም ስላለኝ ብጸልይም በቀላሉ ልባቸው የማይረታ በመሆናቸው ግን ተስፋ ያስቆርጠኛል። ይሁንና አንድ ቀን በአዲስ ልደት ቤ/ክ የሐሙስ የጾም ጸሎት ፕሮግራም ላይ እንደ ልማዴ ልጸልይ ከቤቴ ገስግሼ መጣሁ። በዚያን ቀን በልቤ ያለው ትልቅ ሸክም አባቴ ከ4ት ቀናት በኋላ በ08/27/2018 ሆስፒታል የኦፕራሲዮን ቀጠሮ ስለያዘ፤ የሚፈጠረው አይታወቅምና ጌታን እንዲያገኝ አጥብቄ ልጸልይ ወስኛለሁ። ገና ጉባኤው ውስጥ ስገባ በመንፈስ የተጋጋለ ጸሎት ተቀበለኝ። ...ጆሮዬ ውስጥ ስላልዳኑ ቤተሰቦቻችን እንጸልይ፣ እንናጠቃቸው! እያሉ ጉባኤው  ምልጃም... የተቃውሞም ጸሎትም እያደረገ ነበር።  በመንፈስ ቅዱስ አሠራር ተገርሜ እኔም ቤተስቤን በኃይል እየተናጠቅኩ መጸለዬን ቀጠልኩ። በተለይም ስለ አባቴ ! የዛሬ አንገብጋቢው ርዕሴ ነውና። ጸሎቱ አልቆ ከሰዓት በኋላ  ወደ ጉዳዬ ሄድኩ። ከሶስት ቀናት በኋላ አባቴ ሰርጀሪ ሊያደርግ ሆስፒታል ገባ! ዶክተሩ ክርስቲያን ነበርና ሰርጀሪውን ከመጀመሩ በፊት ተንበርክኮ ጸለየ አለች።  እግዚአብሔር ይመስገን ከሰዓታት በኋላ.. በሰላም ተጠናቆ ወደ ማገገሚያ ክፍሉ ገባ ። ክርስቲያን የሆኑ ነርሶች በየ ክፍሉ እየዞሩ ለበሽተኛ የመጸለይ፣ የተጎዳን የማጽናናት ልማድ አላቸው። ከሰርጀሪው በፊት  አባቴ የተኛበት ክፍል ገብተው "አባባ እንጸልይልዎት? ብለዋቸው  አባቷ " እኔ ኦርቶዶክስ ስለሆንኩ አልፈልግም! " ብለው ነበር። ከ3ት ቀናት በኋላ ግን በ08/30/2018 አባቷ በክርስቲያን ዶክተሩና በነርሶቹ በተደረገላቸው እንክብካቤ ልባቸው ተንክቶ ኖሯልና ነርሶች ድጋሜ ሊጠይቁ ወደ ክፍላቸው ሲገቡ የጠበቃቸው ፊትና ምላሽ እንደፊተኛው አልነበረም። አባባ የእግዚአብሔርን ቃል እናካፍልዎ? እንጸልይልዎ?  አዎ አሉ አባባ! በዚያች ዕለት በደስታ ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ የህይወቴ አዳኝ ነው ብለው መሠከሩ! በሰማይም ታላቅ ደስታ ሆነ! ለአባቷ ጾም ጸሎት ይዛ በ08/23/2018 የጸለየችውም እህት ደስታ አሠከራት! በሐሙስ ጉባኤ ፊት በደስታ ሲቃ ቆማ የጌታን ስራ መሰከረች። ክብር ለእግዚአብሔር ይሁን!  ሃሌ ሉያ!!! ወገኖች ለቤተሰቦቻችን መጸለይና መመስከርን አንርሳ! ይቀጥላል....

<< Let us be witnesses for Christ!>>

No comments:

Post a Comment