Tuesday, November 27, 2018

ወንጌል ያልደረሰው የኢትዮጵያ ክልል!

ወንጌል ያልደረሰው የኢትዮጵያ ክልል!
♦♦♦♦♦♦♦♦♦♦♦
ከአርባ ጊዜ በላይ ስሟ በመጽሐፍ ቅዱስ ላይ የተጠቀሰች፣ የሦስት ሺህ ዓመት ታሪክ እንዳላት የሚወራላት አገራችን ኢትዮጵያ ፤ ወንጌልን በተመለከት ምን ደረጃ ላይ እንዳለች የሚከተለው ዘገባ ያሳያል:-
የውጭ ዜግነት ያላቸው(አሜሪካኖች፣ አረቦች፣ ሱዳኖች፣የመኖች፣ አርመኖች፣ ብሪቲሾች፣ ቻይናውያን፣ ፍሬንቾች፣ ግሪኮች፣ ጣልያኖች፣ አይሁዶች፣ ፓኪስታናውያን፣ ራሺያውያን የሱማሌ) ነዋሪዎችን ጨምሮ፡-      
    ♥113 ብሔር ብሔረሰቦች መኖሪያ.
    ጠቅላላ የሕዝብ ብዛቷ በአሁን ሰዓት 108 ሚሊዮን ይጠጋል ፤ 
    ♥ካቶሊክ፣ኦርቶዶክስ እና ወንጌላውያንን ጨምሮ 59.7% ክርስትና ሃይማኖት አለ፤
    ♥የወንጌል አማኞች ቁጥር 17.03% ደርሷል
    ♥22 ሚሊዮን 33ሺህ ህዝብ ገደማ በወንጌል ያልተደረሰ ህዝብ አላት።/ 20.5% ማለት ነው/
     ♥ወደ 35 ያህል ብሔር ብሔረሰቦች የወንጌል መልዕክት አልደረሳቸውም፤ ይህም በመቶኛ ሲሰላ 31.0 % ይሆናል። ከእነዚህ መካከል በተለይ የእኛ ጸሎትና እገዛ የሚያስፈልጋቸውን ቀጥዬ እዘረዝራለሁ፤ አማኞች ሁላችን በየጸሎት ህብረቱ ላይ፣ በቤተሰብ ጸሎት ጊዜ፣ በቤት ህብረቶች ላይ በግልና በጉባኤ እንድትጸልዩላቸው በጌታ ፍቅር አሳስባለሁ!!!
1.የአፋር ህዝብ = 1,914,000 ብዛት
2.ለአርጎባ ህዝብ= 211,000     >>
3.ለቤንሻንጉል ህዝብ= 313,000
4.ለዳሳናች ብሔር= 72,000
5.ለአላባ ብሔረሰብ = 349,000
6.ለሐመር ህዝብ = 110,000
7.ለአደሬዎች = 48,000
8.ለቀበና ብሔረሰብ = 79,000
9.ለመስቃን ብሔረሰብ = 217,000
10.ለሐረርጌ ኦሮሞ ህዝብ= 5,938,000
11.ለጅማ ህዝብ = 3,350,000
12.ለከረዩ ሕዝብ = 315,000
13.ለወሎ ህዝብ = 345,000
14.ለየጁ ብሔረሰብ = 108,000
15.ለስልጤ ህዝብ = 1,402,000
16.ለሱማሌ ህዝብ= 6,877,000
17.ለሱርማ ብሔረሰብ= 42,000
18.ለጸማይ ማህበረሰብ= 30,000
19.ለቱርካናዎች = 42,000
20.ለዎላን ብሔረሰብ= 130,000 ያህል ናቸው።
ጥናቶች እንደሚያሳዩት ወንጌላውያን አማኞች በኢትዮጵያ ውስጥ በየ ዓመቱ የ4.3% ዕድገት ቢያሳዩም ወንጌል በቋንቋው ካልደረሰው በሚሊዮን የሚቆጠር ህዝብ ጋር ሲነጻጸር ገና ብዙ እንደሚቀረን ያሳያል፤

  ፨ ሁላችን የክርስቶስ ኢየሱስ ምስክሮች እንሁን! በጸሎት፣ በገንዘብና በተለያየ መልክ ወንጌል እንዲሮጥ የበኩላችንን እናድርግ! በእውነት ዋጋችን በሰማይ ታላቅ ይሆናል! ይቀጥላል.....
(ምንጭ:- joshua project .net)

<< LET US BE WITNESSES FOR CHRIST! >>

No comments:

Post a Comment